የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ አገኘሁ ከዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ጋር ተወያዩ

By Melaku Gedif

September 08, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ከዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ስቴቨን ኦማም ዎሬ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በዚሁ ወቅት አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአማራ ክልል አራት ዞኖች በከፈተው ወረራ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸውንና ከ4 ሚሊየን በላይ ዜጎች ደግሞ አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል፡፡