ፋና ስብስብ

ከአንዲት ታካሚ 20 ኪሎ ግራም የሚመዝን እጢ በቀዶ ጥገና ተወገደ

By Feven Bishaw

September 10, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ከአንዲት እናት 20 ኪሎ ግራም የሚመዝን እጢ በተሳካ ቀዶ ጥገና መወገዱ ተሰማ፡፡

ታካሚዋ በሰባት ወራቸው ለእርግዝና ክትትል በመጡበት በማህፀናቸው እጢ መኖሩን ማወቃቸው የተገለፀ ሲሆን÷ የህክምና ባለሙያዎች ለፅንሱ ደህንነት ሲባል ከወሊድ በኋላ ህክምና ለመስጠት መወሰናቸው ተነግሯል።