አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ ቀንን እስከ መስከረም 2 ቀን 2014 ዓ.ም አራዘመ፡፡
ቦርዱ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም ድምፅ ለሚሰጥባቸው የምርጫ ክልሎች ማለትም በሃረሪ ክልል፣ በሶማሌ ክልል የተወሰኑ ምርጫ ክልሎች እና በደቡብ ክልል ምእራብ ኦሞ ዞን የመራጮች ምዝገባን ሲያከናውን መቆየቱ እና የምዝገባው እለትም ዛሬ ጷግሜ 5 ቀን እንደሚጠናቀቅ ይታወሳል።