የሀገር ውስጥ ዜና

አሸባሪው የህወሓት ቡድን ከዛሪማ ከተማ ንብረት እየዘረፈና እያወደመ መሄዱ ተገለፀ

By Feven Bishaw

September 12, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው የህወሓት ቡድን ከዛሪማ ከተማ ሀብትና ንብረት እየዘረፈና እያወደመ መሄዱን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡

አሸባሪው የህወሓት ቡድን ፈንድቃና ዛሪማን ለቆ ሲፈረጥ በዛሪማ ከተማ የንግድ፣ የመንግሥት ተቋማትና እና ሌሎችንም ተቋማት አውድሟል ተብሏል።