አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) በሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የተመራ የብሔራዊ አስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ማዕከል የሚኒስትሮች ኮሚቴ አባላትን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በአፋር ለተፈናቀሉ ወገኖች በጥሬ ገንዘብና በአይነት ከ102 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ፡፡
ልኡካን ቡድኑ ዛሬ ሰመራ ከተማ በመገኘት ድጋፉን ለአፋር ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አወል አርባ አስረክቧል፡፡