የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ ታካሚ የፖሊስ አባላትን ጎበኙ

By Feven Bishaw

September 12, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚስትር ዐቢይ አሕመድ በፌዴራል ፖሊስ ሪፈራል ሆስፒታል ተገኝተው በተለያዩ ግዳጅ ላይ ተሳትፈው ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ የሚገኙ የፖሊስ አባላትን ጎበኙ፡፡

በጉብኝቱ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤልና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሪፈራል ሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡