አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን በአሶሳ ወረዳ በኮሞሽጋ 28 ቀበሌ እና በብልዱጊሉ ቀበሌ በኩታ ገጠም የተዘራ የበቆሎ ማሣን ጎብኝተዋል።
በአሶሳ ወረዳ በ2013/14 ምርት ዘመን ከ85 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን መታቀዱ የተገለፀ ሲሆን ÷ እስከ አሁንም ከ73 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር መሸፈኑን የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደሬጄ አስታውቀዋል፡፡