የሀገር ውስጥ ዜና

በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ከ201 ሚሊየን ብር በላይ ግብይት ተፈፅሟል

By Feven Bishaw

September 13, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ለ2014 የዘመን መለወጫ በዓል ከ201 ሚሊየን ብር በላይ ግብይት መፈጸማቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ህብረት ስራ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

የህብረት ስራ ማህበራቱ በክልሎች ከሚገኙ የግብርናና የኢንዱስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው ቀጥታ የገበያ ትስሰር ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን እንዲያቀርቡ መደረጉን የኤጀንሲው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ጥላሁን ጌታቸው ገልጸዋል ።