አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የ2021 የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ተጀምሯል፡፡ ከምድብ 5 እስከ 8 የሚገኙ ቡድኖች የመጀመሪያ ዙር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ አከናውነዋል፡፡
ምሽት በተካሄደው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ ሲሸነፍ ቼልሲ ድል ቀንቶታል፡፡ የጨዋታዎች ዝርዝር ውጤትም÷
ያንግ ቦይስ ከማንችስተር ዩናይትድን፤ ያንግ ቦይስ 2 ለ 1 ረቷል፣
ሲቪያ ከሳልዝቡርግ፤ 1 አቻ ተለያይተዋል፣
ዲይናሞ ኬቭ ከቤንፊካ፤ ባዶ ለ ባዶ ተለያይተዋል፣
ባየር ሙኒክ ከባርሴሎና፤ ባየር ሙኒክ 3 ለ 0 ረቷል፣
ቪያሪያል ከአትላንታ፤ 2 አቻ ተለያይተዋል፣
ሊል ከ ወልፍስበርግ፤ ባዶ ለባዶ ተለያይተዋል፣
ጁቬንቱስ ከማልሞ፤ ጁቬንቱስ 3 ለ 0 ረቷል፣
ቼልሲ ከዜኒት፤ ቼልሲ1 ለ 0 ረቷል፡፡
ምንጭ ÷ ጎል ዶት ኮም