የሀገር ውስጥ ዜና

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገር ውስጥ ሊገባ የነበረ የኮንትሮባድ እቃ ተያዘ

By Feven Bishaw

September 14, 2021

አዲስ አበባ ፣መስከረም 4፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ባቢሌ ከተማ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የዞኑ ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙዩኒኬሽንና ሚዲያ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ቶሎሳ ጎሹ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ የኮንትሮባንድ እቃዎቹ ትናንት ሌሊቱ ከቦምባስ ከተማ ወደ ባቢሌ ከተማ በአይሱዙ የጭነት ተሸከርካሪ ተጭኖ ሊገባ ሲል ባቢሌ ከተማ መግቢያ ላይ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መያዝ ተችሏል፡፡