የሀገር ውስጥ ዜና

የቦርዱ አመራሮች መስከረም 20 ለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት የመስክ ጉብኝት አደረጉ

By Feven Bishaw

September 14, 2021

አዲስ አበባ ፣መስከረም 4፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች መስከረም 20 ቀን 2014 ምርጫ በሚካሄድባቸውን አካባቢዎች የመስክ ጉብኝትና ውይይት አካሄዱ፡፡

በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የተመራው ቡድን ከደቡብ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር፣ ከዞን አመራሮችንና በአካባቢው ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች ጋር ምርጫውን በተመለከተ ምክክር አካሂዷል።