ዓለምአቀፋዊ ዜና

የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ወደ ቻይና በሚደረጉ ጉዞዎች ላይ እገዳ መጣል ተገቢ አለመሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ገለፀ

By Tibebu Kebede

February 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ወደ ቻይና በሚደረጉ ጉዞዎች ላይ እገዳ መጣል ተገቢ አለመሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ገለፁ።

በቻይና የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመግታት ሀገራት ወደ ሀገሪቱ የሚደረጉ ጉዞዎችን እያገዱ፣ የንግድ ግንኙነቶችን እያቋረጡ እና አየር መንገዶችም ጉዞ እየሰረዙ መሆኑ ይታወቃል።