የሀገር ውስጥ ዜና

አብዛኞቹ የሰበአዊ አርዳታ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ከመቐለ አልተመለሱም – የዓለም ምግብ ፕሮግራም

By Tibebu Kebede

September 16, 2021

 

አዲስ አበባ ፣መስከረም 6፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰበአዊ አርዳታ ጭነው መቐለ የገቡ አብዛኞቹ ተሽከርካሪዎች አልተመለሱም ሲል የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታወቀ።

በዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ቢሮ እንዳስታወቀው የዕርዳታ እህል እንዲያደርሱ 466 የጭነት ተሽከርካሪዎች ወደ መቐለ ቢላኩም የተመለሱት 38ቱ ብቻ ናቸው።

ቢሮ እንደሚለው ለትግራይ ህዝብ የሰበአዊ አርዳታ ለማድረስ ተሽከርካሪዎች እንደሚያስፈልጉት ገልጾ ጉዳዩ እንዳሳሰበው አስታውቋል።

አሸባሪው ህወሓት ተሽከርካሪዎችን በመውሰድ ለጥፋት ተግባሩ መፈፀሚያ እያዋላቸው እንደሆነ የሚያሳዪ መረጃዎች ከሳምንታት በፊት ሲወጡ ነበር።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!