የሀገር ውስጥ ዜና

“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት” የትዊተር ዘመቻና የማህደር ምስል ዛሬ ይቀየራል

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ ፣መስከረም 7፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ)”የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት” የትዊተር ዘመቻና የማህደር ምስል ዛሬ ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ከ7 ደቂቃ ላይ የመቀየር መርሃ ግብር እንደሚካሄድ የዘመቻው ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ።

የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ተጠቃሚ ኢትዮጵያዊያን በተጠቀሰው ሠዓት የማህደር ምስላቸውን /ፕሮፋይል ፒክቸር/ የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት በሚል በተዘጋጀው እንዲቀይሩም ጥሪ ቀርቧል።