አዲስ አበባ ፣መስከረም 7፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች የኢትዮጵያን እውነታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ የተጀመረውን “ነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት” ዘመቻን ፊርማቸውን በማኖር አስጀምረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ÷የህወሓት የሽብር ቡድን ከ10ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ላይ ጉዳት በማድረስ ከ3ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ እንዲሆኑ አድርጓል ብለዋል።