የሀገር ውስጥ ዜና

የነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት ዘመቻ በሽብርተኛው ህወሓት ከትምህርት ገበታቸው ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ይወክላል- ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ ፣መስከረም 7፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች የኢትዮጵያን እውነታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ የተጀመረውን “ነጩ ፖስታ ለነጩ ቤተመንግስት” ዘመቻን ፊርማቸውን በማኖር አስጀምረዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ÷የህወሓት የሽብር ቡድን ከ10ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ላይ ጉዳት በማድረስ ከ3ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ እንዲሆኑ አድርጓል ብለዋል።