የሀገር ውስጥ ዜና

ትግራይ ሥርዓት አልበኝነት የሰፈነባት የስቃይ ማዕከል ሆናለች – ትዴፓ

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ትግራይ ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ልጆች ወደ ጦርነት የሚጋዙባትና ሥርዓት አልበኝነት የሰፈነባት የስቃይ ማዕከል ሆናለች ሲሉ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቱ (ትዴፓ) የፖለቲካ ጉዳዮች ምክትል ሃላፊ አቶ ተስፋዬ አለማየሁ ተናገሩ።

አቶ ተስፋዬ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ትግራይ ትምህርት ቤቶችና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እስር ቤት የሆኑባት የአፍሪካ ጓንታናሞ ሆናለች ብለዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-