የሀገር ውስጥ ዜና

የውሀ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል በአሸባሪው ህወሓት ጥቃት ለወደሙ መሰረተ ልማቶች ጥገና የሚውል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሀ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል በአሸባሪው ህወሓት ጥቃት ለወደሙ የውሀና የሀይል አገልግሎት መሰረተ ልማት ጥገና የሚውል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉን ለክልሉ ርዕሠ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር ያስረከቡት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በወረራው ለዜጎች የውሀ እና የሀይል አገልግሎት የሚሠጡ ተቋማት ወድመዋል፤ በዚህም ዜጎች ችግር ገጥሟቸዋል ብለዋል።