አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሀ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል በአሸባሪው ህወሓት ጥቃት ለወደሙ የውሀና የሀይል አገልግሎት መሰረተ ልማት ጥገና የሚውል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።
ድጋፉን ለክልሉ ርዕሠ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር ያስረከቡት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በወረራው ለዜጎች የውሀ እና የሀይል አገልግሎት የሚሠጡ ተቋማት ወድመዋል፤ በዚህም ዜጎች ችግር ገጥሟቸዋል ብለዋል።