የሀገር ውስጥ ዜና

ጀርመን ከ271 ሺህ ዶዝ በላይ የኮቪድ-19 ክትባት ለኢትዮጵያ ድጋፍ አደረገች

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመን መንግስት 271 ሺህ 200 ዶዝ አስትራዜኒካ የኮቪድ-19 ክትባትና 900 ሺህ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛለኢትዮጵያ ድጋፍ አደረገ፡፡

በኢትዮጵያ የጀርመን ምክትል አምባሳደር ሄይኮ ኒሽኬ ክትባቱን ለጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስረክበዋል።