የሀገር ውስጥ ዜና

ህብረተሰቡ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን መከላከያዎችን በአግባቡ ሊተገብር ይገባል-የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ አስተዳደር የኮቪድ -19 ወረርሽኝ እንደ አዲስ በመቀስቀሱ ህብረተሰቡና የትምህርት ተቋማት የመከላከያ መንገዶችን በአግባቡ እንዲተገብሩ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ አሳሰበ።

በተያዘው ሳምንት ብቻ በኮሮና ቫይረስ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተመልክቷል፡፡