የሀገር ውስጥ ዜና

በሀገሪቱ 2 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ ተጨማሪ ስንዴ ይመረታል -ግብርና ሚኒስቴር

By Feven Bishaw

September 17, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከውጭ የሚገባውን የስንዴ ምርት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት 2 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ ተጨማሪ ስንዴ ለማምረት እንደሚሰራ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ የ2013 የግብርና ሥራ አፈፃፀምና የተያዘው የስራ ዘመን አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ አካሂዷል ፡፡