አዲስ አበባ ፣መስከረም 7፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መነሻውን ደሴ በማድረግ ባህርዳር ከተማ ላይ 14 ሺህ የክላሽ ጥይት በቁጥጥር ዋለ።
በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 3:30 ሰዓት መነሻውን ደሴ በማድረግ በመካነሰላም መርጦ ለማሪያም ሞጣ ባ/ዳር መስመር የታርጋ ቁጥር ኮድ3 አአ 59582 የሆነ ሲንግል ካፕ መኪና ሻግ በማሰራት 14 ሺህ የክላሽ ጥይት በደብቅ ሲጓጓዝ ባ/ዳር ከተማ ቀበሌ 14 ሁሴን አህመድ እና መሃመድ አደም ከተባሉ ተጠርጣሪዎች ጋር እጅ ከፍንጅ ከክልሉ ፓሊስ አባላት ጋር በጋራ በመሆን በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከመነሻዉ ደሴ ጀምሮ እሰከ መዳረሻዉ ባ/ህርዳር ከተማ ሚስጥራዊ ክትትል በማድረግ ለክልሉ ፖሊስ ጥቆማና መረጃ በመስጠት ተጠርጣሪዎች እንዲያዙና ህገወጥ የግንኙነት መረቡ እንዲበጣጠስ ያደረገዉ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ነዉ፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!