አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቻይና ዩናይትድ ኢንቨስትመንት ቡድን በአዲስ አበባ የኢንዱስትሪ መንደር የመገንባት ፍላጎት እንዳለው ገለፀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር አክሊሉ ሀይለሚካኤል በኢንቨስትመንት ቡድኑ ፕሬዚዳንት ሰሂቼንግ ዣንግ ከተመራው ልኡክ ጋር በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት እድሎች፣ የኢትዮጵያ መንግስት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች እና በኢንቨስትመንት ቡድኑ ፍላጎት ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።