የሀገር ውስጥ ዜና

ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ያስተላለፉትን ትዕዛዝ ሊሰርዙ ይገባል

By Feven Bishaw

September 19, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ያስተላለፉትን ትዕዛዝ ሊሰርዙት እንደሚገባ የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ጠየቀ።

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያን ሁኔታ ያልተገነዘበ ነው ያለውን የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የማዕቀብ ትዕዛዝ አጥብቆ እንደሚያወግዘው አስታውቋል።