የሀገር ውስጥ ዜና

ፍትሃዊ፣ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ ፓርቲዎች ህግን መሰረት ያደረገ እንቅሰቃሴ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

February 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፍትሃዊ፣ ተኣማኒ፣ ነጻ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ በቅድመ ምርጫ ወቅት ፓርቲዎች ህግን መሰረት ያደረገ እንቅሰቃሴ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ።

ከፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የኮሙዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ፥ ቦርዱ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በሚፈለገው ደረጃ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።