በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአማራ ባለሃብቶች ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አደረጉ

By Tibebu Kebede

September 19, 2021

 

አዲስ አበባ ፣መስከረም 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአማራ ባለሃብቶች ለመከላከያ ሰራዊትእና ለክልል ልዩ ሃይሎች ድጋፍ አደረጉ።

ባለሃብቶቹ 1ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ዋጋ የሚያወጡ 40 ሰንጋዎችን ነው በማይጠብሪ ግንባር የሽብር ቡድኑን እየተፋለመ ለሚገኘው መከላከያ ሠራዊት ፣ ለክልል ልዩ ሃይሎች እና ሚሊሻዎች ነው ድጋፍ ያደረጉት።

በተጨማሪም 1ሺህ የሚሆኑ አልባሳትን በግንባሩ ለሠማሩ የጸጥታ ሃይሎች ድጋፍ አድርገዋል።

በለሃብቶቹ በቀጣይም ለመከላከያ ሰራዊት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

በመላኩ ገድፍ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!