የሀገር ውስጥ ዜና

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አመራርና ሰራተኞች 9 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አደረጉ

By Feven Bishaw

September 20, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አመራርና ሰራተኞች 9 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አድርገዋል፡፡

በርክክብ ስነ ስርዓቱ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ዳምጠው እንዳሉት÷ ተቋሙ የህዝብ ሚዲያ መሆኑን ለማረጋገጥ ልማትን በማገዝና የህዝብ ፍላጎቶችን በማስጠበቅ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።