የሀገር ውስጥ ዜና

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች “ነጩ ፖስታ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” ንቅናቄን ተቀላቀሉ

By Feven Bishaw

September 20, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች “ነጩ ፖስታ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” ንቅናቄን ተቀላቅለዋል፡፡

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ኢትዮጵያ በአለም አደባባይ ያላትን ተቀባይነትና ገጽታ ለማበለሻት ግንባር ፈጥረው እየተንቀሳሰቀሱ ያሉ ሃይሎችን ለመቀልበስ ነጩ ፖስታ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት በሚል በተዘጋጀው ዘመቻ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራርና ሰራተኞች ላሳዩት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡