አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን በጦር ግንባር በመገኘት የሚሰሯቸው ዘገባዎች እውነታን በማውጣትና የህወሓት የሽብር ቡድኑንን እውነተኛ መልክ በማሳየት ላይ እንደሚገኙ በዘገባ የተሳተፉ ባለሙያዎችና የጦር መኮንኖች ተናገሩ፡፡
የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋዜጠኛ ዙፋን ካሳሁን ከጀግኖች ጋር ውሎ በማደር ለህዝቡ እውነተኛ መረጃን ማድረስ ሙያዊ ሀላፊነትን መወጣት እንደሆነ ተናግራለች፡፡