የሀገር ውስጥ ዜና

የቁሳቁስ ስርጭት ስራ ተጠናቋል-ቦርዱ

By Feven Bishaw

September 21, 2021

አዲስ አበባ፣መስከረም 11፣2024 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

ቦርዱ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም በሐረሪ ፣ ሶማሌ እና ደቡብ ክልል ለሚያካሂደው ምርጫና ሕዝበ ውሣኔ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ነው ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ ያጠናቀቀው፡፡