አዲስ አበባ፣መስከረም 11፣2024 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡
ቦርዱ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም በሐረሪ ፣ ሶማሌ እና ደቡብ ክልል ለሚያካሂደው ምርጫና ሕዝበ ውሣኔ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ነው ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ ያጠናቀቀው፡፡