የሀገር ውስጥ ዜና

ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ በቂ የፀጥታ ዝግጅት መደረጉን ፖሊስ አስታወቀ

By Tibebu Kebede

February 05, 2020

አዲስ አበባ፣ጥር 27፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ በቂ የፀጥታ ዝግጅት ማድረጉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ በያዝነው ሳምንት በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 33ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ በቂ የጸጥታ ጥበቃ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል።