የሀገር ውስጥ ዜና

የአይሳይታ-አፋምቦ- ጅቡቲ ድንበር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ተጀመረ

By Tibebu Kebede

February 05, 2020

አዲስ አበባ፣ጥር 27፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) በ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የሚገነባው የአይሳይታ-አፋምቦ- ጅቡቲ ድንበር የአስፋልት መንገድ ግንባታ መጀመሩን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።

የአስፋልት መንገድ ግንባታው መንግስት በመደበው 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተጀመረ ሲሆን፥ በሶስት ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል፡፡