የሀገር ውስጥ ዜና

የ”ሄር ኢሴ” ባህላዊ ህግ በአለም ቅርስነት ለማስመዘገብ እንቅስቃሴ ተጀመረ

By Feven Bishaw

September 23, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)”ሄር ኢሴ” የኢሣ ማህበረሰብ ባህላዊ ያልተጻፈ ህግ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት ፣የሣይንስና የባህል ድርጅት/ዩኒስኮ/ ለማስመዝገብ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ፣የጅቡቲና የሶማሌ ላንድ የኢሣ ማህበረሰብ አባቶች የተሣተፉበት በባህላዊ ህጎች ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ በድሬደዋ ተካሂዷል።