የሀገር ውስጥ ዜና

በመስቀል በዓልም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ርችት መተኮስ የተከለከለ ነው- ፖሊስ

By Feven Bishaw

September 24, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በመስቀል በዓልም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ርችት መተኮስ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

በበዓላት ወቅት የሚተኮሱ ርችቶችን ሽፋን በማድረግ ሰላምን የማደፍረስ ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች በህገ-ወጥ መንገድ የገዙትን የጦር መሣሪያ እንደሚፈትሹና የተለያዩ የፀጥታ ስጋቶችን እንደሚፈጥሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡