የሀገር ውስጥ ዜና

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለአገር መከላከያ ሰራዊት 284 የእርድ እንስሳትና 40 ኩንታል ስንቅ ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

September 24, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለአገር መከላከያ ሰራዊት 284 የእርድ እንስሳት እና 40 ኩንታል ስንቅ ድጋፍ አደረገ።

ከክልሉ ከተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ህብረተሰቡ ያዋጣውን ድጋፍ የአገር ሽማግሌዎችና የማህበረሰብ ተወካዮች ለአገር መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።