የሀገር ውስጥ ዜና

የሲዳማ ክልል ሰዉ ሃበት ልማት ቢሮ በ2013 ዓ.ም የተሻለ አፈጻጸም ላላቸው መዋቅሮች እዉቅና ሰጠ

By Feven Bishaw

September 28, 2021

አዲስ አበባ፣መሰከረም18፣2014 (ኤፍ ቢሲ)የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የተሻለ አፈፃፀም ላላቸው መዋቅሮች እና ግንባር ቀደም ፈፃሚዎች ዕውቅና የመስጠት ስነ-ስርዓት ተካሄደ።

በመርሐ ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ፣የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረፅዮን አበበ ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሁሉም ከተሞች እና ወረዳዎች አስተዳዳሪዎችና የፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።