ዓለምአቀፋዊ ዜና

ደቡብ ሱዳን እና ኡጋንዳ በመካከላቸው የነበረውን የዜጎች የጉዞ ቪዛ አስቀሩ

By Meseret Awoke

October 05, 2021

አዲሰ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኡጋንዳውያንና ደቡብ ሱዳናውያን ወደየአገሮቹ ጉዞ ሲያደርጉ ይጠየቅ የነበረውን ቪዛ ማስቀረታቸው ተገለጸ።

ኡጋንዳ ቀደም ሲል በመስከረም ወር የቪዛ ጥያቄን ያስቀረች ሲሆን÷ ደቡብ ሱዳንም በተመሳሳይ ኡጋንዳውያን ያለቪዛ እንዲገቡ ፈቅዳለች፡፡

የደቡብ ሱዳን ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደንግ ዳው ደንግ እንዳረጋገጡት÷ ሀገራቸው ውሳኔውን ያሳለፈችው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥያቄን ተከትሎ ነው፡፡

ደቡብ ሱዳን በቅርቡ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ሃገራትን የተቀላቀለች ሲሆን÷ በሃገራቱ መካከል ባለው ስምምነት የሰዎች እና የሰራተኛ ነፃ ዝውውርን ያበረታታል፡፡

ኡጋንዳ፣ ኬኒያ፣ ታንዛኒያ፣ ርዋንዳ እና ብሩንዲ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ሀገራት ናቸው፡፡

ደቡብ ሱዳን የአፍሪካ ማህበረሰብን የተቀላቀለችው እ.አ.አ በ2016 ሲሆን÷ የጋራ ገበያ የመሳሰሉ የማህበረሰብ ተግባራትን ለመቀላቀል ዘግይታለች፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!