የሀገር ውስጥ ዜና

በመንግስት ቀዳሚ አጀንዳነት የሰላምና ደህንነት ጉዳይ መካተቱ አስፈላጊ ነው – ምሁራን

By Feven Bishaw

October 05, 2021

አዲስ አበባ፣መስከረም፣25፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በመንግስት ቀዳሚ አጀንዳነት የሰላምና ደህንነት ጉዳይ መካተቱ ተጠባቂም አስፈላጊም ነው ሲሉ የህግ ምሁራን ተናገሩ፡፡

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግስት የኢትዮጵያን ህልውና ማስቀጠልን፣ ሰላምና ደህንነትን ማስጠበቅን ቀዳሚ ትኩረት በመስጠት የፀጥታ ሀይሉን የማደራጀት ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡