አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው ልዑክ በዱግዳ ወረዳ በ10 ሄክታር መሬት ላይ በክላስተር የሚመረተውን የፓፓዬ ማሳ በመጎብኝት አርሶ አደሮችን አበረታቷል፡፡
እንደ ኦሮሚያ ክልል በ 1ሺህ 200 ሄክታር መሬት ላይ የፓፓዬ ምርት እየተመረተ እንደሚገኝ የክልሉ ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ጌቱ ገመቱ ተናግረዋል፡፡