አዲስ አባባ፣ መስከረም 28፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የተማሪዎች ምገባ መርሃ-ግብር ተግባራዊ መሆን በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ወደ ትምህርት ገበታ የሚመጡ ተማሪዎችን ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ አስታወቀ።
ኤጀንሲው በዘንድሮው ትምህርት ዘመን ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመያዝ በሁሉም የቅድመ መደበኛና የመጀመሪያ ደረጃ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ምገባ ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁንም ገልጿል።