የሀገር ውስጥ ዜና

ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ አርሶ አደሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀም እየተደረገ ነው-የምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ

By Feven Bishaw

October 08, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2014 ( ኤፍ ቢ ሲ)ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ አርሶ አደሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀም እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የዞኑ ግብርና መምሪያ ሃላፊ እና ባለሙያዎች እንዲሁም ሞዴል አርሶ አደሮች በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ በክላስተር የተዘራ የጤፍ እና ስንዴ ማሳን ጎብኝተዋል።