አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱ የመንግስት አስተዳደር ለብዙ ጊዜ ስር የሰደደውን ሌብነት ለመቆጣጣር ቅድሚያ ሰጥቶ መስራት እንዳለበት የህግ እና የፀረ ሙስና የማህበረሰብ አንቂ ምሁራን ተናገሩ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የፀረ ሙስና የማህበረሰብ አንቂና የህግ አማካሪው አቶ ክብረ አብ አበራ÷ ባለፉት ዓመታት የመንግስት ባለስልጣናት በተሳተፉበት ሁኔታ በሚፈጸም ሌብነት በርካታ የሀገር ሀብት ተዘርፏል ።