የሀገር ውስጥ ዜና

130 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ሰሊጥ ወቅቱን ባለጠበቀ ዝናብ እንዳይጎዳ እየተሰበሰበ ነው

By Feven Bishaw

October 14, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ጎንደር ዞን ለውጭ ገበያ የሚቀርብ በ130 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ሰሊጥ ወቅቱን ባልጠበቀ ዝናብ እንዳይጎዳ በመሰብሰብ ላይ እንደሚገኝ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

እየተሰበሰበ ያለው የሰሊጥ ምርት ከህልውና ዘመቻው ጎን ለጎን በ2013/14 ምርት ዘመን በባለሃብቶችና አርሶ አደሮች የለማው ነው።