የሀገር ውስጥ ዜና

በዝናብ እጥረት ምክንያት በተከሰተ ድርቅ ለችግር መጋለጣቸውን የቦረና ዞን ነዋሪዎች ተናገሩ

By Feven Bishaw

October 15, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዝናብ እጥረት ምክንያት በተከሰተ ድርቅ ለውሀ፣ለምግብና ለጤና ችግር መጋለጣቸውን የቦረና ዞን ነዋሪዎች ተናገሩ።

በዞኑ በ2013 ዓ.ም የበልግ ዝናብ በቂ አለመሆኑና የ2014 ዓ.ም የመኸር ዝናብ በወቅቱ ባለመዝነቡ ምክንያት በሰውና በእንስሳት ላይ ጉዳት እየደረሰ መሆኑንም የቦረና ዞን አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሬባ ኦዳ ገልፀዋል።