የሀገር ውስጥ ዜና

የቤልጅየም ም/ጠ/ሚ እና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለአቶ ደመቀ መኮንን የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት ላኩ

By Feven Bishaw

October 15, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፖላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዚቢግናዉ ራዬና የቤልጅየም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሶፊያ ዊልሚስ ለአቶ ደመቀ መኮንን የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ሶፊያ ዊልሚስ÷ አቶ ደመቀ መኮንን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው ባስተላለፉት የደስታ መልዕክት አዲሱ መንግስት በሁለቱ አገራት መካከል ያለዉን ወዳጅነት ለማስቀጠል በአለም አቀፍ፤ ቀጠናዊ እና በአካባቢው ጉዳዮች ላይ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።