በአስተዳደሩ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማዋ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ ለጋዜጠኞች ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት፥ በመሬት ወረራ እና ዝርፊያ ላይ የተሰማሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ እና በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ባለፉት ወራት የማጥራት ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
የደረጃው ያሉ የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት ማኔጅመንት የቢሮ ኃላፊዎች ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ማድረግን ጨምሮ ዝርዝር ማስረጃዎችን በመንተራስ በፍትህ አካላት በወንጀል እንዲጠየቁ የማድረግ ሂደት መጀመሩንም ገልጸዋል።
ሕገወጥ የመሬት ወረራውን ለመከላከል ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ፣ የአርሶ አደሩን መብት ሽፋን በማድረግ መብቱ ለማይገባቸው አካላት የይዞታ ማረጋገጫ የሰጡና መታወቂያ የሰሩ ከክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚ እስከ ወረዳ ድረስ በሚገኙ አመራሮች ላይ እርምጃው መቀጠሉንም ጠቁመዋል።