የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ሰፊ የኢንቨስትመንትአማራጮች እንዳሉ የውጭ ኩባንያ ተወካዮች መሰከሩ

By Feven Bishaw

October 15, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት የሚያስችሉ አማራጮች እንዳሉ ማጤናቸውን የውጭ ኩባንያ ተወካዮች ተናገሩ።

ከ40 በላይ የተለያዩ የውጭና የአገር ውስጥ ኩባንያዎች የተሳተፉበት አራተኛው የኢትዮጵያ የግብርና፣ ምግብና መጠጥ ማቀነባበርና የፕላስቲክ ህትመት የንግድ ትርኢት በአዲስ አበባ ተከፍቷል።