የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን ኢትዮጵያ ድጋፏን ትቀጥላለች

By Feven Bishaw

October 15, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት አተገባበር የክትትልና ግምገማ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር ሜጀር ጄኔራል ቻርለስ ታይን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ምክትል ሊቀ-መንበሩ አቶ ደመቀ ዳግም በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት በማስተላለፍ፤ የደቡብ ሱዳንን ግጭት ለማስቆም በተፋላሚዎች መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነትን አተገባበርን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡