አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት አተገባበር የክትትልና ግምገማ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር ሜጀር ጄኔራል ቻርለስ ታይን ጋር ተወያይተዋል፡፡
ምክትል ሊቀ-መንበሩ አቶ ደመቀ ዳግም በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት በማስተላለፍ፤ የደቡብ ሱዳንን ግጭት ለማስቆም በተፋላሚዎች መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነትን አተገባበርን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡