የሀገር ውስጥ ዜና

በጎንደር ከተማ በህገ ወጥ ድርጊት በተሳተፉ የፀጥታ አካላት ላይ እርምጃ የመወስዱ ተግባር ይቀጥላል

By Feven Bishaw

October 17, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ በህገ ወጥ ድርጊት በተሳተፉ የፀጥታ አካላት ላይ እርምጃ የመወስዱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዘውዱ ማለደ ተናገሩ፡፡

በከተማዋ የሚፈፀመውን ህገወጥ ድርጊት የመከላከል እና የፀጥታ ሁኔታውን ወደ መደበኛ ሁኔታ የመመለስ ተግባር አዲስ የተዋቀረው ካቢኔ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ነው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በተለይ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬት ተናገሩት፡፡