የሀገር ውስጥ ዜና

119 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እጽ ተያዘ

By Feven Bishaw

October 19, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በጉጂ ዞን የአዶላ ሬዴ ወረዳ በሞተር ብስክሌት ሲጓጓዝ የነበረ 119 ኪሎ ግራም የሚመዝን አደንዛዥ እጽ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አብዱልከሪም ሁሴን እንደገለጹት፤ አደንዛዥ እጹ የተያዘው ምሽት ላይ ወደ ነገሌ ከተማ ሲጓጓዝ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ ነው፡፡