አዲስ አበባ፣ጥቅምት 9፤2014 (ኤፍ ቢሲ) የኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፖሊስ የጋራ የፀጥታ ግብረ ሀይል የአሸባሪዎቹን የሸኔና የህወሓት የጥፋት ተልዕኮ ለማምከን በጋራ እየሰሩ መሆኑን አስታወቁ።
የየክልሎቹ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እንዳመለከቱት፤ ከአሸባሪው ህወሃት ጋር በመናበብ በህዝብ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ያለውን አሸባሪው ሸኔ የሚፈጽመውን ድርጊት ለማስቆም የክልሎቹ የጋራ የፀጥታ ግብረ ሀይል ህዝብን ያሳተፈ ዘመቻ እያደረገ ነው።