የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የፀጥታ የጋራ ግብረ ሀይል የአሸባሪዎቹን ሸኔና ህወሓት የጥፋት ተልዕኮ ለማምከን እየሰራ ነው

By Feven Bishaw

October 19, 2021

አዲስ አበባ፣ጥቅምት 9፤2014 (ኤፍ ቢሲ) የኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፖሊስ የጋራ የፀጥታ ግብረ ሀይል የአሸባሪዎቹን የሸኔና የህወሓት የጥፋት ተልዕኮ ለማምከን በጋራ እየሰሩ መሆኑን አስታወቁ።

የየክልሎቹ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እንዳመለከቱት፤ ከአሸባሪው ህወሃት ጋር በመናበብ በህዝብ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ያለውን አሸባሪው ሸኔ የሚፈጽመውን ድርጊት ለማስቆም የክልሎቹ የጋራ የፀጥታ ግብረ ሀይል ህዝብን ያሳተፈ ዘመቻ እያደረገ ነው።